Showing posts with label Ethiopia people. Show all posts
Showing posts with label Ethiopia people. Show all posts

Wednesday, November 13, 2013

ዳግማዊ ሠለሞን!

መቼም ስለ መርካቶ ያልተወራ ነገር ያለ አይመስለኝም….መርካቶን የማያውቃት ይኖራል ለማለትም አልደፍርም፡፡ ከአፍሪካ በስፋቱ ተወዳዳሪ ያልተገኘለት ትልቁ የገበያ ማህከል፡፡መርካቶ!
ስለ መርካቶ ሎሬት ፀጋዬ ገ/መድህን በግጥም ‹‹አይ መርካቶ›› ተወዳጁ አብዱ ኪያር በዜማ ‹‹መርካቶ ሰፈሬ›› ና ወዘተ የብዙ የጥበብ ሰዎች እጅ ዳሷታል፡፡
እኔ የምለው መርካቶ ውስጥ ካሉ ቦታዎች አውቶብስ ተራ አካባቢ የሚገኘውን አዲስ ከተማ ት/ቤትን አስተውለውት ያውቃሉ?
የቀድሞ ልዑል መኮንን የአሁኑ አዲስ ከተማ መሠናዶ ት/ቤት የሠፈረበት አካካባቢ አስገራሚ ገፅታ ያለው ቦታ ነው፡፡ ት/ቤቱን ለተመለከተው እንዴት ሰው ሊማርበት ይችላል ብሎ ሊገረም እንደሚችል ጥርጥር የለኝም፡፡ እመኑኝ በድፍን ኢትዮጵያ እንደ አዲስ ከተማ አስገራሚ ት/ቤት አይኖርም፡፡
ቀን በእውቀት የታነፁ የአገር ተረካቢዎችን ለማፍራት የሚታትረው ት/ቤት ማታ ማታ በብዙ እንስቶች ተከቦ ይታያል፡፡
አንዳንዴ ዝም ብዬ ስመለከተው ጠቢቡ ሰለሞንን የሆነ ይመስለኛል፡፡ ምክንያቱም ሁለቱም በሴት የመታጀባቸው ጉዳይ ነው፡፡
የዘመኑ ሰለሞን አዲስ ከተማ አመሻሽ ላይ ልጅነታቸውን ባልጨረሱ ወጣት ሴቶች ተከቦ ማየቱ የተለመደ ነው፡፡

Saturday, May 25, 2013

የቡርቃ ዝምታ የተሰኘውን መፅሐፍ በነፃ ያነቡት

ጋዜጠኛና ደራሲ ተስፋዬ ገብረአብ 
ከታዋቂውና ዝነኛው ጋዜጠኛና ደራሲ ተስፋዬ ገብረአብ መፅሐፎች ውስጥ የቡርቃ ዝምታ የተሰኘውን መፅሐፍ በነፃ ያነቡት ዘንድ ተጋብዘዋል፡፡

Wednesday, April 24, 2013

የኢሰፓ ሊቀመንበር የነበሩት ኮሎኔል መንግስቱ በልብ በሽታ .መሞት.....



menegestu
Mengestu h/mariam with Fidel kastero
የዛሬ የማህበራዊ ድህረ ገፅ ወሬዎች በቀድሞ የኢሰፓ ሊቀመንበር በነበሩት ኮሎኔል መንግስቱ ሃ/ማርያም ሆኗል፡፡ ኮሎኔሉ በልብ በሽታ እነደሞቱ ጥቂት የማይባሉ የማህበራዊ ድህረ ገፅ ታዳሚዎች መርዶውን እየነገሩን ነው፡፡ የኮሎኔሉን መሞት መንግስት ከዘረጋው መልካም አስተዳደር የመነጨ ስለመሆኖም አንዳንዶች እየደሰኮሩ ስንሰማ ባላንጣችንን ሞት ክብር ላንተ እንድል አስገድዶናል፡፡ መንግስቱ ደግም ሰሩ ክፉ የዚህች ድሃ አገር ገዥ ሆነው ለ 17 አመታት ኖረዋል፡፡ በመሞታቸው መደሰት ሳይሆን እንሲቪላይዝድ ሰው ቤተሰባቸውን ባናፅናናም ክፉ መናገሩን በበኩሌ የማልደግፈው ነው፡፡ አትዮጵያ ባትቀድምም አትዮጵያ ትቅደምን እንድናዜም ያረጉ ሶሻሊስት ኢትዮጵያን ለመገንባት ግንባር ድረስ የሄዱ ትጉህ ወታደር ኋላም ጥሩ ፈርጣጭ ነበሩና የእውነት ሞተው እንኳን ቢሆን ነብሳቸውን ይማርልን ብለን ኢትዮጵያዊ ጨዋነታችንን እናሳይ እላለው፡፡

Sunday, April 14, 2013

አበሻ ኩሩ ነው!?

የትኛው አበሻ? የድሮው ወይስ የአሁኑ? እውን በምናችን ይሆን እንዲ አበሻ ኩሩ ነው በሚል ብሂል ውጥርጥር ያልነው፡፡ ቲሸርቶቻችን የሚናገሩት ስለኩሩነታችን፤ስለጀግንነታችንና ስለብዝሃነታችን ከሆነ ሰንበትበት ብሏል፡፡ኩሩ ማህበረሰብ ለራሱ የተለየ ቦታ ያለውና ሌሎች ላይ የማይደርስ በሎሎች የተከበረ ለመሆኑም የማህበረሰብ ሳይንስ ሊቃውንት የሚስማሙበት አቅ ነው፡፡
የአበሻ ኩሩነት እንደቻይናውያን እንቁራሪት አለመብላቱና ምግብ መምረጡ ከሆነ ኩሩነት ትርጉሙ መቀየር አለበት ባይ ነኝ፡፡ ኩሩነታችን አለመንበርከካችንና በነጭ አለመገዛታችን  ነው የምንል ከሆነ ደግሞ ለዚህ ዘመን አበሾች የማይመጥን ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ ነጮች እንደዋዛ ክብራችንን ከነጠቁን ዘመናት አለፉ....በቱሪስት መዳረሻ በሆኑ ከተሞቻችን  ኩሩው አበሻ ለፈረንጆች የሚያሳየውን ፍቅር ስንመለከት ሰውኛ የሆነ የጨዋ ሕዝብ ልዩ ምልክት መሆኑን እንታዘብና ወደራሳችን ተመልሰን ጓዳችንን ስናይ የሰውኛ ባህሪ መሆኑ ይጠፋብንና አድር ባይነታችን ይጎላብናል፡፡ ሴቶቻችን የአበሻ ወንድ በአፍንጫዬ ካሉም ሰንበትበት ብለዋል...ቄሶቻችን በቤተ እምነት መዘክር ውስጥ ‹‹ፈረንጅ መቷል ውጡ›› ማለት ከጀመሩም አመታት አለፉ፡፡ ማለፍ ክልክል ነው፤መንገዱ ዝግ ነው በሚባሉ ቦታዎች ላይ አበሾች ተኮልኩለው ነጭ እንደዋዛ ሲያልፍና ፍቃድ ሲሰጠው ስናይ ልማታዊነታችን ታውሶን በቸልታ የምናልፈው የእለት ተእለት ተራ ጉዳይ ከሆነም ሰንብቷል፡፡ ኩሩነት በአባቶች ታሪክ መታበይ ከሆነ እውነት ኩሩ አለመሆናችንን ላስረግጥ እወዳለው፡፡
የአበሻ ኩሩነት በጎዳና የወደቀውን ወንድሙን የሚያንቋሽሽና አለውልህ ከማለት የኘጮችን በጎነት የሚናፍቅ እከሌ እኮ እስፖንሰር አግኝቶ....የምንል የጉድ ልጆች ከንቱ ኩራት... ሲረግጡን የምንረገጥ የራሳችን ማንነት የጠፋብን ተአምር ጠባቂዎች፤የምላስ ቁማርተኞች፤ሆዳችን ክብራችን የሆነ ዘመነኛ ኩሩዎች!
ወዳጄ ኩሩ ነኝ ብለህ ታስባለህ? እንግዲያውስ ለራስህ ቦታ ይኑርህ፤እራስህን አክብር፤ በቆዳ ልዩነት የማታምን ቅድሚያ ለኢትዮጵያዊው ወንድሜ የሚል አትዮጵያዊ ብሔርተኛ ሁን!!
በዚህ ርዕሰ ጉዳይ ላይ ወደፊት በሰፊው እናወጋለን፡፡

Sunday, February 10, 2013

ሃ/ማርያም ሆይ ጫማው ሰፍቶዎታል!!!

ሃ/ማርያም ሆይ ጫማው ሰፍቶዎታል!!!

የሠዎች አስተሳሰብ በኖሩበት ማህበረሰብ እንዲሁም በግለሰባዊ ማንነት ላይ ተመርኩዞ የተለያየ እንደሚሆን እሙን
ነው፡፡ከአንድ ማህፀን በወጡ ሁለት መንትያ ልጆች መካከል እንኳን የሚኖረው የአስተሳሰብ ልዩነት ስንመለከት ሠዎች
በየትኛውም መለከኪያ ተመሳሳይ የሆነ የአስተሳሰብ ደረጃ ሊኖራቸው እንደማይችል እንረዳለን፡፡ በአንድ ነገር ላይ
ተመሳሳይ አቋም ቢኖረንም ነገሩን የምንረዳበት መንገድና የአፈፃፀሙ ሁኔታ ከሰው ሰው ተለያይቶም እንመለከታለን፡፡
የአብዮታዊ ዲሞክራሲ ልሂቃን የሆኑት መሪዎቻችን በአንድ ልብ እናስብ በአንድ ቃል እናውራ ብለው መነሳታቸው
ምናልባትም በመንፈሳዊ ሕይወታችን የምናውቃቸው የቤተክርስቲያን ሊቃውንት ሰልስቱ ምዕት እንደ አንድ ልብ አሳቢ
እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ በመሆን በቤተክርስቲያን ላይ ክህደት የፈፀሙትን ሰዎች አውግዘው እንደነበር ድርሳናት
ያወሱትን እንድናስታውስ ይጋብዘናል፡፡ መቼም መለኮታዊ ሃይል ካልዳሰሰን በቀር ሠዎች በአመለካከትና በአነጋገር
ፍፁም አንድ ሆነው ያለአሳብ ልዩነት ነገሮችን ሊወስኑ እንደማይችሉ በቤተሰብ ውስጥ በሚወሰኑ ውሳኔዎች እንኳን
መታዘብ እንችላለን፡፡(ፈላጭ ቆራጭ አባወራ ካልሆነ፡፡)
ላለፉት 20 እና 21 አመታት ውስጥ በኢትዮጵያ ፓርላማ ውስጥ ነገሮች ሲወሰኑ መለኮታዊ ሃይል የዳሰሳቸው ይመስል
ያለ አንዳች ክርክርና ተቃውሞ ውሳኔዎች ሲወሰኑ አይተናል፡፡መቼም ያለአሳብ ልዩነት ጥሩ ነገር ማግኘት አይቻልም
እንዲሁም የተሻለውን መወሰን ፍፁም ከባድ መሆኑንና ተከትሎት የሚመጣውም ውጤት አስደሳች እንደማይሆን መረዳቱ
አስቸጋሪ አይሆንም፡፡ አምባ ገነኖች ለሚያነሱት አሳብ ተቃውሞን እንደማይሹ የፓርላማ ውስጥ ሽሙጥና ዘለፋ ምስክር
ነው፡፡በአለም ላይ ስልጣን የያዙ አምባገነን መሪዎች ሁሉ ተመሳሳይ የሚያደርጋቸው ባህሪ ቢኖር ለሕብረተሰቡ
እናውቅልሃለን፤እኛ ከሌለን…የሚሉ ፈሊጦችን በአደባባይ መፎከር ነው፡፡አብዮታዊ መሪዎቻችን ቢሆኑም ለኢትዮጵያውያን
እናውቅልሃለን ከማለት ውጭ ፍላጎታችንን ጠይቀውን አያውቁም፡፡በየቀበሌው የሚደረገው ሕብረተሰባዊ ተሳትፎ
የሚያሰፈልገው ስብሰባም ቢሆን ፖለቲካዊ ፋይዳው እንጂ ለህብረተሰቡ የሚያስገኘው አንዳችም ኢኮኖሚያዊም ይሁን
ማህበራዊ ጥቅም እንደሌለ ኑሮዋችን በቂ ምስክር ነው፡፡
የሆነው ሆኖ መጤው ጠ/ሚንስትር የቀድሞውን ጠ/ሚንስትር ጫማ በማጥለቅ የግል ባህሪያቸውንና ውስጣቸው የተደበቀውን
ሃይል እያጠፉ ያለ ይመስለኛል፡፡ ሠው እንደራሱ እንጂ እንደጎረቤቱ አይኖርም የሚለው ኢትዮጵያዊው ብሂል እዚህ
ጋር ወሃ ቋጥሮ እናገኘዋለን፡፡አቶ ሃ/ማሪያም እንደራሳቸው እንጂ እንደ አቶ መለስ ሊመሩን ከቶውንም አይገባም፡፡
እንደሚታወቀው የአቶ መለስ ጥንካሬ ፓርቲያቸውን ጠንካራ ከማድረግ አልፎ የሚኒሊክን ቤተ መንግስት የግላቸው
እስከማድረግ አድርሷቸዋል፡፡ ደግም ይሁን ክፉ በታጋዩ ፈርሆን የግል አመለካከትና ጥንካሬ አገሪቷ ላይ ለ21
አመት  ያሻቸውን ሲፈፅሙ እንደነበር የወራት ትዝታችን መሆኑን ከሞቱ በኋላ በትግል ጓዶቻቸው
ተመስክሮላቸዋል፡፡አቶ መለስ ከአልባኒያን ስርዓት እስከ ልማታዊ መንግስትነት ያደረሳቸው የራሳቸው የግል
አመለካከትን በለሌች ላይ በተለይ በትግል ጓዶቻቸው ላይ የማሳረፍ ታለቅ ተሰጥሆ ስለነበራቸው ነው፡፡(የአብዮታዊ
ዲሞክራሲ ልሂቃን ትግላቸው የአልባኒያ አይነት ስርዓት በኢትዮጵያ ለማምጣት እንደነበር የምንዘነጋው
አይደለም፡፡የሚገርመው ነገር መገንባት የሚፈልጉት ስርሃት ጨቋኝ በሚባለው መንግስቱ እንኳን የማይደገፍ መሆኑ
ነው፡፡በወቅቱ አልባኒያ በሆጃዎች ትመራ የነበር ፍፁም አምባ ገነንነት የሰፈነባት አገር ነበረች፡፡)