Friday, January 16, 2015

አንድ…ሶስት




አራት በአራት በሆነች ክፍል ውስጥ ረሃ እየሆኑ ነው፡፡ አንዱን ሲጥሉ አንዱን ሲያነሱ ታላቅ የአሳብ ባህር ውስጥ ገብተው ስለሕይወት ይፈላሰፉ ጀምረዋል፡፡ የፊት ገፅታቸው ተቀያይሯል….አይኖቻቸው ልውጣ ልውጣ የሚሉ ይመስላሉ፡፡ ፈጠዋል፡፡ የቤቱ ሙቀት የሲጋራው ጢስ ታክሎበት ፊትን ይጋራፋል፡፡ ሶስት ብቻ በመሆናቸው ተጠባብቆ ለማውራት አመችቷቸዋል፡፡የማህበረሰቡን ወግ መኮነን ተያይዘውታል፤ከግለሰብ ማንነታቸው ጋር ሊሄድ ባልቻለው ማህበረሰብ ውስጥ ተፈጥረው ማድረግ የፈለጉትን የሞራል ሕግ በሚል ጠፍሮ የያዛቸውን የቡድን ሕግ በማውገዝ ላይ ናቸው፡፡ ሞራል ደካሞችና ፈሪዎች ጠንካሮችን የሚያስሩበት ሰንሰለት መሆኑን መተማመን ችለዋል፡፡ The only good man is the man who succeeds የምትለዋ የኒቼ አሳብ አጥንታቸው ድረስ ዘልቆ ተሰምቷቸዋል፡፡ አሸናፊዎች ሁሌም ጉዞ ላይ ናቸው፤በጉዞው የደከሙትና መረሳት ያልፈለጉት የሞራልን ጉዳይ በማንሳት በጉዞዋቸው ርቀው እንዳይሔዱ ያደርጋሉ በዚህም በማህበረሰብ ውስጥ የሚበቅሉ አሸናፊዎች ነገራቸው ሁሉ ከማህበረሰቡ አመለካከት አንጻር እየተለካ ለውግዘትና ለመገለል ያበቃቸዋል፡፡
      ትምህርቷን ከአስራ ሁለተኛ ክፍል አቋርጣ ቤት ብትውልም መፅሐፍትን የማንበብ ክፉኛ መንፈስ ተጠናውቷታል፡፡ ማንንም ተናግሮ ማሳመን የተካነችው ለግላጋዋ ወጣት በሁለት ወንዶች መሃል ወሲብን ማውራት የቀለለ ተራ ነገር አድርጋዋለች፡፡ የሁለቱን ወጣቶች ጆሮ ለጉድ ተቆጣጥራዋለች፡፡ ታወራለች፤ይሰሟታል፡፡
‹‹ሴክስ ትልቁ መደሰቻዬ ነው፤በወሲብ የማገኘው እርካታ ፍፁም ነው›› ከአዳም ወገን የሆኑት አዳማውያን ተፋጠጡ፡፡ ከሄዋን ዘር ሰምተውት የማያውቁትን ቁም ነገር ሄዋን እየነገረቻቸው ነው፡፡ ለቁም ነገሩ ድምቀት ሲጃራውን ከጠረጼዛው ላይ አንስቶ አቀጣጠለው፡፡ ቤቱ ጊዜያዊ የጢስ ጉም ሰርቷል፡፡ ከደብዛዛው መብራት ጋር ስፔስ ውስጥ ብቻቸውን ያሉ አስመስሏቸዋል፡፡ ድንቅ አለም፡፡ ገጅኒ ትራሱን አደላድሎ የከንፈሩን ዳርቻዎች በጣቶቹ ካፀዳ በኋላ  አመለካከቱን ይሰነዝር ጀመር፡፡
‹‹ ከእናንተ ከሴቶቹ ይልቅ ወንዶቹ ነን በወሲብ ላይ የነቃነው፤የወሲብን ደስታንም በሚገባ ያጣጣምነው…ሴቶች ሁሌም ስሜታቹን የምትደብቁት ከወሲብ የሚገኘው ደስታ ሁሌም የኛ መስሎ ስለሚሰማቹ ነው፡፡ ስለዚህ መደሰት የምትችሉትን ያህል አትደሰቱም፡፡›› ሮቤራ ነቃ ማለት ጀመረ፡፡ በጠቶቹ መሃል አጣብቆ የያዘውን ሲጃራ ለሔዋን አቀብሏት እሱም የተሰማውን መተንተን ጀመረ፡፡
‹‹ወሲብ ስትፈፅሙ እንኳን መነቃቃት እንጂ ማነቃቃቱን ትሳቀቁበታላቹ…ገና ለገና ወሲባም እባላለው ብላቹ ስለምታስቡ መጠቃትን ምርጫቹ አደረጋቹ፡፡ ምናልባትም በማጥቃት ላይ ያለውን ደስታም ልታጣጥሙ አልቻላቹም፡፡›› ሔዋን ቱግ አለች፡፡ አፏ ውስጥ የነበረውን ጢስ ተግሞጥሙጣው ወደላይ ተፋችው፡፡
‹‹በማጥቃት ላይ ያለውን ደስታ የነጠቃቹን እናንተ ወንዶች እንጂ ተፈጥሯችን አይደለም፡፡ ወሲብን የኛ አድርገን እንዳናስበውና እንዳንደሰትበት ፍላጎታችን ባልሆነበት ሁኔታ እየነካካቹን እንዴት እንድንፍታታበት ትጠብቃላቹ? አለም ላይ ያለው ወንዳዊው ስርሃት ሴቶችን ከራሱ ፍላጎት አንፃር እንጂ በማንነታችን መች ተመልክቶን ያውቃል? በቅዱሳን መፅሐፍት እንኳን ሳይቀር የፈቱ ሴቶችን ያገባ አጢያት እንደሰራ ተደርጎ ይወሰዳል….ምናልባት ስሜቷን ያልተረዳላት ወንድ አግብታ ብተፈታው ይህች እንስት እድሜ ልኳን መበለት እንድትሆን እንጂ ሁለተኛ እድል የምታገኝበት ሁኔታ የለም ማለት ነው፡፡ አለም ላይ ያለው ስርሃት ፍፁም ወንዳዊ በመሆኑና ራሱን ፍፁም አድርጎ በማሰቡ ሴቶችን ከራሱ ፍላጎት አንፃር ያያል፡፡ የሚገርመው ነገር በስነፍጥረት እንኳን ወንድ መቅደሙንና ሴትም ከወንድ መገኘቷን ብንመለከት ወንዱ ለራሱ የሰጠው ግምት ምን ያህል እንደሆነ ያሳያል…ሲጃራውን በሀይል ወደሳንባዋ ምጋው ወደጣራው ተፋችው፡፡ ‹‹ ሴቶች በነገር ሁሉ እየተገዙና በዝግታ ይኑሩ፤ልታስተምር አሊያም በወንድ ልትሰለጥን አትችልም የሚለው ቅዱስ ትህዛዝ እንኳን ብንመለከተው ምንያህል ነፃነታችንንና ማንነታችንን ጠፍሮ እንደሚይዘው አስቡት….ማድረግ የፈለግነውን እንዳናደርግ ሁሉም ነገር ከወንዶች አንፃር ተመዝኗል….በእርግጠኝነት ይህ ትህዛዝ ከፈጣሪ ለመሆኑ እጠራጠራለው…..ወሲብ አንዱ ነፃነታችን ነው ነገር ግን ይህን ስሜት ለዘመናት እየገደላቹብን ነበር….ግርዛት እንኳን መነሻው ወንዳዊው አለም ለወሲብ ያለውን የተዛባ አመለካከት የሚያሳይ ነው፡፡›› ሔዋን ልቧ በሀይል ይመታል፡፡ አፋቸውን አዘጋቻቸው፡፡ መልከ መልካሙ ሮቤራ ሞጋች አሳቡን በማንሰላሰል ላይ ነው፡፡ አሳብ ከጫቱ ቅጠል ይፈልቅ ይመስል በጣቱ ይፈትገዋል፡፡ ገጅኒ ፀጉሩን እያፍተለተለ ባዘጋጃት ቀጭን ደረቅ የጫት እንጨት ጥርሱን ይጎረጉራል፡፡
‹‹አጥቂነታቹን ማንም አልነጠቃቹም፡፡ ማጥቃት አለመቻላቹ ነው፤ተፈጥሯቹ በሙሉ ድብቅ በመሆኑ በጥቃት በተደበቀው ነገር እንደሰታለን….መደሰቻቹ ግልፅ ሆኖ አለመታየቱ በራሱ ድብቅ ተፈጥሯቹን ይናገራል…አንድ ወንድና ሴት እርቃናቸውን ቢቆሙ እንኳን ሁሉን ነገር በግልፅ ልታዪ የምትችይው ወንዱ ላይ ነው፡፡›› ሮቤራ ነበር ተናጋሪው፡፡ ሔዋን ተቅበጠበጠች…መጠቃት የመረጣቹት እናንተ ናቹ ያላትን አንስታ በአሳቡ ያልረጋ መሆኑን በጨዋ አማርኛ ገለፀችለት፡፡ ግልፅነትን የገለፀበት መንገድ አናቶሚን ያላገናዘበና ተፈጥሮንም ቢሆን ግምት ውስጥ ያላስገባ እንደሆነ በአንፃራዊነት ሕግ ለማስረዳት ሞከረች፡፡ ገጅኒ ወደሮቤራ እየተመለከተ ፈገግ አለ፡፡ በጣቱ ያሻት የነበረችውን የጫት ቅጠል ገረባው ላይ ቀላቅሎ ‹‹መጠቃትን መረጣቹ ማለቴ ማጥቃትና መጠቃት ምርጫ ሆኖ አይደለም፡፡ ማጥቃትም መጠቃትም ተፈጥሯዊ ሊሆን አይችልም፡፡ ነገር ግን በወሲብ ወቅት እንኳን ሴቷ እራሷን እያመቻቸች መደሰት ሲገባት በወንዱ ትህዛዝና የፍላጎት አለንጋ ትጠቃለች….ወሲብ የጋራ ከሆነ ሴቶችም የወንዶችን ያህል ወሲብ ላይ አስተዋፅኦ ማድረግ መቻል አለባቸው፡፡ ግልፅነትንም ያነሳውት እንዳልሽው ድብቅና ግልፅ የሆነውን የሰውነት ክፍል ለመግለፅ ብቻ ሳይሆን ስሜትን ካለመግለፅ ጋር አያይዘዤ ነው….በእርግጥ በወንዶች ስርሃት የምትመራዋ አለም ሴቶች ላይ ያደረሰችው የሞራል ክስረት ሊለካ የማይችል ነው….በዚህ ስርሃት ውስጥ ደግሞ ነፃ ልትወጡ የምትችሉት በወንዱ መልካም ፍቃድ ሳይሆን በራሳቹ ትግል ነው….ትግሉ ስሜትን በማዳመጥ እራሳቹን በመሆን የምታገኙት ነው የሚመስለኝ›› ሔዋን ደስ አላት….የወንዳዊው ስርሃት ሴቶችን ተፈጥሯቸው እስኪመስላቸው ድረስ ተብትቦ መያዙን ስታስበው ደግሞ አናደዳት፡፡ ገጅኒ የሚፈትለውን ፀጉር ትቶ ጣቶቹን አየር ላይ እያብላላቸው…‹‹የትኛውም ወንድ ወሲብ ፈፅሞ የሚናደድ የለም፡፡ማድረግ ፈልጎ ስለሚያደርግ ሁሌም ፈታ ይልበታል፤ተያይዞ የሚመጣበት ነገር ካሌለ በቀር ሁሌም ደስተኛ ነው፡፡ ብዙዎቻቹ ግን ከወሲብ በኋላ የመጨነቅና ባላደረኩ የሚል ክፉ አሳብ ተጠናውቷችኋል፡፡ after sex ደውለሽ እንኳን ስለማታው መደሰትሽን ብትገልጪላት ወሬውን ለማዞር ስትታትር ነው የምታያት…..እና እናንተ ወሲብን እየተደሰትንበት ነው ብላቹ ታስባላቹ?… ካደረኩትም በኋላ በነፃነት ስለማወራው እንደናንተ የሚገርፈኝ የፀፀት አለንጋ የለም›› ሔዋን የከነከናት ነገር ያለ ይመስላል፡፡ እየተብሰለሰለች ነው፡፡
‹‹ተያይዞ ለሚመጣው ነገርም አላፊነቱን ከእኛ እኩል ልትወስዱ ይገባል፡፡ አለበለዚያ ግን ደስታችንን ሼር አድርገናቹ ቀጥሎ የሚመጣውንም ነገር የመቀበል የሞራል ወኔው ከሌላቹ አሁንም የወንዶች ስርሃት በሆነው አለም ላይ ሴቷ ነች ተበዳይ…ደስታችን ሙሉ የሚሆነው የገነባቹትን አጥር ማፍረስ ስትችሉ ነው፡፡ እንዳንተ አመለካከት እኛ ሁሌም ለእናንተ መጠቀሚያ እንጂ እናንተም ለኛ እንደምታስፈልጉን አትረዱትም፤ይህን መረዳት ብትችሉ ወሲብ ለሁለታችነም እኩል ደስታን ይሰጠን ነበር…ሴቶችም ቢሆኑ እንደሚፈልጉት በመሆን ደስታቸውን ባጣጣሙም ነበር›› ሮቤራ ለሔዋን አስተያየት ግድ የሰጠው አይመስልም…ወደገጅኒ እየተመለከተ…‹‹በመሰረቱ ሊፀፅትህ የሚችለው ነገር አስገድደህ በግዳጅ የምታደርገው ነገር ሊሆን ይገባል፡፡ አስገድደህ አይፀፅተኝም መለቱ እብደት ነው…በግዳጅ ውስጥ ሁሌም ጉልበት አለ፡፡ ወሲብ አስደሳች ከሆነ ደስታዬን በጉልበት ሌሎችን ጨቁኜ ማግኘት አልችልም፡፡ በመፈቃቀድ ላይ ያደረከው ፈታ ሊያደርግህ ይገባል…ደስታህም ሙሉ ይሆናል፡፡›› ሮቤራ ተናግሮ ኮካውን ወደአፉ አስጠጋው፡፡ ሔዋን መሬቱ ላይ አንዳች ነገር የምትፈልግ ትመስላለች፡፡ ቀና ብላ ሮቤራን ተመለከተችው፡፡ ‹‹አንዲት ሴት ካንተ ጋር ወሲብ መድረግ እፈልጋለው ብትልህ ምላሽህ ምንድን ነው?›› ሮቤራ ድንገተኛ የሔዋን ጥያቄ ግራ አጋባው፡፡
‹‹ከኔ ጋር የጠበቀ ግንኙነት ያሌላት ሴት ይህን ትጠይቃለች ብዬ ለማሰብ ይከብደኛል…የማደርገው አይመስለኝም!››ፈገግ አለች….‹‹ ሴክስ ማድረግ አፈልጋለው!››
ሁሉም ተያዩ፡፡ አዳማውያን የደም ትቧቸው ወፍሯል፡፡ ሮቤራ የግንባሩ ደም ስር የፊደል ቅርፅ ሰርቷል፡፡ በፍጥነት ከአልጋው ላይ ተነሳች፡፡ ቀሚስዋን ወደታች እየጎተተች    ‹‹ወሲብ መዝናኛችን ነው ብላቹ ካሰባቹ እንዝናና›› ወደገጅኒ ፊትዋን አዞረች…እራሱን በመናጥ እሺታውን ገለፀላት፡፡ ሮቤራ እንቅስቃሴ አይታይበትም…አንጋጦ አይን አይኗን ይመለከታታል፡፡ እጆቿን ሰታው ገጅኒን ወደራሷ ሳበችው፡፡ አፏ ውስጥ ያለውን ደቃቃ ጫት ማስታጠቢያው ላይ ተፍታው ወደሮቤራ ተመለከተች፡፡ ገጅኒ ያደረገችውን አደረገ…የአንቦውሃ ጠርሙሱን አንስቶ ውሃውን ተጎነጨው፡፡ አፋቸውን አፀዱ፡፡ ሁለቱም ቁልቁል ሮቤራን ተመለከቱት፡፡ ማድረግ አለመፈለጉን የሚገልፅበት ቃላት አጥቶ ምላሱ ተሳሰረበት፡፡……ሔዋን የገጅኒ ወፍራም ከንፈር ላይ ከንፈሯን ለጠፈቻቸው…እጆቿ ፊቱን ከበው ይዘውታል፡፡ ምላሷን አጎረሰችው፡፡ ጠብቶ መለሳቸው፡፡ ሮቤራ ከተቀመጠበት ፊቱን ወደበሩ አዙሮ ተነሳ….ሔዋን እጁን ያዘችው…ወደራሷ አስጠግታ ከንፈሩን በከንፈሯ አራሰችው፡፡ ‹‹አንተም ይመለከትሃል››
‹‹ ኖ! የቡድን ወሲብ አይመቸኝም›› ሮቤራ በዝግታ መለሰላት፡፡
‹‹እሺ ማድረግ ባትፈልግም ይህን ቤት ለቆ መውጣት አይቻልም፡፡ በሴክስ የምትደሰት ከሆነ ሼም የሚባለውን ነገር ሴክስ ላይ ማሳየት የለብህም….በምትደሰትበት ነገር እንዴት ታፍራለህ?›› ወደጆሮው ተጠግታ ነገረችው፡፡ ሮቤራ ተስማማ…ወደተነሳበት ሄዶ ሲጃራውን አቀጣጥሎ ቀጣይ ያለውን ትህይንት ለማየት ተቀመጠ፡፡ ሔዋን የገጅኒን ቀበቶ መፍታት ጀመረች፡፡ በቁማቸው መተሻሸት….ምላስ መጎራረስ….ሮቤራ በሲጃራው ጢስ ውስጥ የሚሆነውን ይከታተላል፡፡ ስሜታቸው ጦዟል…ገጅኒ እርቃኑን ነው….ሔዋን ፍም ገላዋ የገጅኒን ሰውነት ታኮ ቆሟል….አልጋ ላይ ወደቁ….ገጅኒ ከታች ሔዋን ከላይ….ሮቤራ ተቁነጠነጠ….አናቱ አተኮሰው…ሲጋራውን መተርኮሻው ላይ ወርውሮት ተሸርቱን ማወላለቅ ጀመረ፡፡

No comments:

Post a Comment