Sunday, December 22, 2013

የሮበርት አንቶኔ ሕይወትን የመቀየሪያ ምስጢሮች

የአንድ ሺህ ማይል ጉዞ መጀመሪያው አንድ እርምጃ ነው የሚለውን አባባል ሰምተው ሊሆን ይችላል፡፡ እርሶም ይህን አንድ እርምጃ በመጀመርሆ እንኳን ደስ አልዎ!
እንደብዞዎች አኗኗር ስልት ከሆነ ሕይወትዎ በጣም የተጨናነቀና ውጥረት የበዛበት ነው፡፡ ቢሆንም እባክሆ ለሚቀጥሉት ስድስት ቀናት ጊዜዎት ሰተውኝ ይህን ፅሁፍ ያንብቡልኝ፡፡
ምን አልባት ነገሬን ሳልጀምር ስለምን ላወራ እንደሆነ ገምተው አሊያም ሙሉ በሙሉ አውቀውት ሊሆን ይችላል፡፡ እባክሆ ሙሉ ፅሁፉን አንብበው ሳይጨርሱ ምንም አይነት ፍርድ ለመስጠት አይቸኩሉ፡፡
እንጀምር…..
ነገሬን በጥያቄ ልጀምር " ይህን ፅሁፍ ለምን እንደሚያነቡት ያውቃሉ?"
ምንአልባት መልስዎ ሊሆን የሚችለው "ባጋጣሚ ብሎግህን ሰርች ሳደርግ አግኝቸው ነው" አሊያም "ጓደኛዬ ስለዚህ ፅሁፍ መረጃ ሰቶኝ ነው" ወይም የተለያዩ አመክኖአዊ መልሶችን ሊሰጡኝ ይችላሉ፡፡
ዋናው ነገር መልስዎ አመክኖአዊ ይሁንም አይሁንም ይህን ፅሁፍ የሚያነቡበት መሰረታዊ ነገር እንዳለ እሙን ነው፡፡ አንድ ነገር እየፈለጉ ነው! ነገር ግን እስከ አሁን ድረስ በእይወትዎ ላይ ሊያመጣ ያለውን ነገር አላስተዋሉትም፡፡
ይህ ፅሁፍ ለእርስዎ የሚሰጠው አንድ ነገር አለ ምናልባት በንግድ፤በጤናዎ፤በፍቅር እይወትዎ አሊያም ሊታይ የማይችል የአይምሮ ደስታ፡፡
አዕምርዎ በሕይወትዎ  ውስጥ የፈለጉትን ሊያገኙበት የሚችሉበት ዋንኛውና ትልቁ ጉልበትዎ እንደሆነ እስከ አሁን አልነገርኮትም፡፡ ሁሉም ሰው ጭንቅላት አለው ነገር ግን ስለምን አዕምሯቸውን ተጠቅመው የሚያልሙትን ሕይወት መኖር ተሳናቸው?
ለምን ብዙ ሰዎች የአዕምሯቸውን ጉልበት ለራሳቸው ከመጠቀም ይልቅ እራሳቸውን ለማጥፊያነት ይጠቀሙበታል? መልሱን ከጥቂት ደቂቃ በኋላ ያገኙታል፡፡ ትግስትዎ አይለየኝ፡፡