Tuesday, November 28, 2017

የሂወት ዎጋው ስንት ነው?

ከእለታት ባንዱ ቀን አንድ ታዳጊ አባቱን “የህይወት ዋጋው ስንት ነው?” ሲል ጠየቀው፡፡ አባትም መልስ በመስጠት ፈንታ ልጁን እንዲህ ሲል አዘዘው፡፡ “እንካ ይህንን የድንጋይ ቁራጭ...ወደ ገበያ ውሰደው፡፡ ሰዎችም ዋጋውን ከጠየቁህ በጣቶችህ ሁለት ቁጥርን ብቻ አሳያቸው እንጂ ምንም አትናገር” አለው፡፡ ልጁም ድንጋዩን ወሰደ፡፡ ወጥቶም በገበያ መሃል ቆመ፡፡ አንዲት ሴትም መጣች፡፡ “ይህ ድንጋይ ዋጋው ስንት ነው? ብትሸጥልኝ ወስጄ ግቢዬ ውስጥ አስቀምጠዋለሁ” አለችው፡፡ ልጁም እንደታዘዘው ምንም ሳይናገር ሁለት ጣቶቹን አሳያት፡፡ እሷም አለች “ሁለት ብር?
እወስደዋለሁ!!”
ልጁም ወደ ቤቱ ተመለሰ፡፡ በገበያ ያጋጠመውንም ለአባቱ ነገረው፡፡
አባትየውም አለው “አሁን ደግሞ ድንጋዩን ይዘህ ወደ ሙዚየም ሂድ፡፡ ዋጋውን ሲጠይቁህም ሁለት ጣቶችህን አሳይ”፡፡ ልጁም ወደ ሙዚየም ወጣ፡፡ ገዢም መጥቶ ዋጋ በጠየቀው ጊዜ ሁለት ጣቶቹን አሳየው፡፡ ገዢውም “ሁለት መቶ ብር? እወስደዋለሁ!” አለው፡፡ ልጁም በድንጋጤ ወደ ቤቱ ተመለሰ፡፡ ያጋጠመውንም ለአባቱ ነገረው፡፡
አባትየውም ተናገረ፡፡ “አሁን ደግሞ በመጨረሻ ድንጋዩን ይዘህ ወደ የከበሩ ማዕድናት መሸጫ ሂድ ለባለቤቱም አሳየው”
አለው፡፡ ልጁም ሄደ፡፡ ለሱቁም ባለቤት አሳየው፡፡ የሱቁ ባለቤት በመገረም “ይህ እኮ አለም ላይ እጅግ ውድ ከሆኑ የከበሩ ድንጋዮች አንዱ ነው” አለ፡፡ “ከየት አገኘኸው? ስንትስ ትሸጠዋለህ?” ሲል ጠየቀው፡፡ ልጁም ምንም ሳይናገር ሁለት ጣቶቹን አሳየ፡፡
የሱቁም ባለቤት አለ.... “ይህንን ድንጋይ በሁለት መቶ ሺህ ብር እወስደዋለሁ፡፡”
ልጁም በመገረም እየሮጠ ወደ ቤቱ ተመልሶ ያጋጠመውን ለአባቱ ነገረው፡፡
አባትየውም “ልጄ አሁን የህይወትህ ዋጋ ተገልጦልሃል” አለው፡፡
አየህ የመጣህበት ቦታ፣ ዘርህ፣ ሃይማኖትህ፣ የቤተሰቦችህ ሃብት፣ የተወለድክበት ቦታ ልዩነት አይፈጥርም፡፡ ዋናው ራስህን የምታስቀምጥበት ቦታ፣ ራስህን የምታገኝበት የሰዎች ስብስብ ነው፡፡ ልዩነቱ ያለው ራስህን ለመሸከም በምትመርጥበት መንገድ ነው፡፡ ህይወትህን ሙሉ የሁለት ብር ድንጋይ ዋጋ ስትሰጠው ኖረህ ይሆናል፡፡ ህይወትህን ሙሉ የኖርከው ዋጋህ ሁለት ብር ብቻ እንደሆነ በሚያስቡ ሰዎች ተከበህ ይሆናል፡፡ ነገር ግን እያንዳንዱ ሰው ውድ የሆነ የከበረ ድንጋይ በውስጡ ይዟል፡፡ ልዩነቱም ያለው ውስጣችን
ያለውን የከበረ ድንጋይ አይተው ዋጋ በሚሰጡን ሰዎች መሃል መገኘትን ስንመርጥ ነው፡፡ ራሳችንን በገበያ ወይም በከበሩ ማዕድናት ሱቅ የማስቀመጥ ምርጫው አለን፡፡ በሌሎች ሰዎች ውስጥ ያለውንም ውድ ዋጋ ለማየት ምርጫው የኛው ነው፡፡ ሌሎች ሰዎችም የከበረ ዋጋቸውን እንዲረዱ ማድረግ
እንችላለን፡፡ አብረህ የምትውላቸውን ሰዎች በጥንቃቄ ምረጥ፡፡ ይህ በህይወትህ ልዩነትን ይፈጥራልና፡፡
.
ሻውን ቡንደናሂራን ከተረከው የተተረጎመ
ምንጭ ፡ የኔታ ቱዩብ

የሂወት ዎጋው ስንት ነው?

ከእለታት ባንዱ ቀን አንድ ታዳጊ አባቱን “የህይወት ዋጋው ስንት ነው?” ሲል ጠየቀው፡፡ አባትም መልስ በመስጠት ፈንታ ልጁን እንዲህ ሲል አዘዘው፡፡ “እንካ ይህንን የድንጋይ ቁራጭ...ወደ ገበያ ውሰደው፡፡ ሰዎችም ዋጋውን ከጠየቁህ በጣቶችህ ሁለት ቁጥርን ብቻ አሳያቸው እንጂ ምንም አትናገር” አለው፡፡ ልጁም ድንጋዩን ወሰደ፡፡ ወጥቶም በገበያ መሃል ቆመ፡፡ አንዲት ሴትም መጣች፡፡ “ይህ ድንጋይ ዋጋው ስንት ነው? ብትሸጥልኝ ወስጄ ግቢዬ ውስጥ አስቀምጠዋለሁ” አለችው፡፡ ልጁም እንደታዘዘው ምንም ሳይናገር ሁለት ጣቶቹን አሳያት፡፡ እሷም አለች “ሁለት ብር?
እወስደዋለሁ!!”
ልጁም ወደ ቤቱ ተመለሰ፡፡ በገበያ ያጋጠመውንም ለአባቱ ነገረው፡፡
አባትየውም አለው “አሁን ደግሞ ድንጋዩን ይዘህ ወደ ሙዚየም ሂድ፡፡ ዋጋውን ሲጠይቁህም ሁለት ጣቶችህን አሳይ”፡፡ ልጁም ወደ ሙዚየም ወጣ፡፡ ገዢም መጥቶ ዋጋ በጠየቀው ጊዜ ሁለት ጣቶቹን አሳየው፡፡ ገዢውም “ሁለት መቶ ብር? እወስደዋለሁ!” አለው፡፡ ልጁም በድንጋጤ ወደ ቤቱ ተመለሰ፡፡ ያጋጠመውንም ለአባቱ ነገረው፡፡
አባትየውም ተናገረ፡፡ “አሁን ደግሞ በመጨረሻ ድንጋዩን ይዘህ ወደ የከበሩ ማዕድናት መሸጫ ሂድ ለባለቤቱም አሳየው”
አለው፡፡ ልጁም ሄደ፡፡ ለሱቁም ባለቤት አሳየው፡፡ የሱቁ ባለቤት በመገረም “ይህ እኮ አለም ላይ እጅግ ውድ ከሆኑ የከበሩ ድንጋዮች አንዱ ነው” አለ፡፡ “ከየት አገኘኸው? ስንትስ ትሸጠዋለህ?” ሲል ጠየቀው፡፡ ልጁም ምንም ሳይናገር ሁለት ጣቶቹን አሳየ፡፡
የሱቁም ባለቤት አለ.... “ይህንን ድንጋይ በሁለት መቶ ሺህ ብር እወስደዋለሁ፡፡”
ልጁም በመገረም እየሮጠ ወደ ቤቱ ተመልሶ ያጋጠመውን ለአባቱ ነገረው፡፡
አባትየውም “ልጄ አሁን የህይወትህ ዋጋ ተገልጦልሃል” አለው፡፡
አየህ የመጣህበት ቦታ፣ ዘርህ፣ ሃይማኖትህ፣ የቤተሰቦችህ ሃብት፣ የተወለድክበት ቦታ ልዩነት አይፈጥርም፡፡ ዋናው ራስህን የምታስቀምጥበት ቦታ፣ ራስህን የምታገኝበት የሰዎች ስብስብ ነው፡፡ ልዩነቱ ያለው ራስህን ለመሸከም በምትመርጥበት መንገድ ነው፡፡ ህይወትህን ሙሉ የሁለት ብር ድንጋይ ዋጋ ስትሰጠው ኖረህ ይሆናል፡፡ ህይወትህን ሙሉ የኖርከው ዋጋህ ሁለት ብር ብቻ እንደሆነ በሚያስቡ ሰዎች ተከበህ ይሆናል፡፡ ነገር ግን እያንዳንዱ ሰው ውድ የሆነ የከበረ ድንጋይ በውስጡ ይዟል፡፡ ልዩነቱም ያለው ውስጣችን
ያለውን የከበረ ድንጋይ አይተው ዋጋ በሚሰጡን ሰዎች መሃል መገኘትን ስንመርጥ ነው፡፡ ራሳችንን በገበያ ወይም በከበሩ ማዕድናት ሱቅ የማስቀመጥ ምርጫው አለን፡፡ በሌሎች ሰዎች ውስጥ ያለውንም ውድ ዋጋ ለማየት ምርጫው የኛው ነው፡፡ ሌሎች ሰዎችም የከበረ ዋጋቸውን እንዲረዱ ማድረግ
እንችላለን፡፡ አብረህ የምትውላቸውን ሰዎች በጥንቃቄ ምረጥ፡፡ ይህ በህይወትህ ልዩነትን ይፈጥራልና፡፡
.
ሻውን ቡንደናሂራን ከተረከው የተተረጎመ
ምንጭ ፡ የኔታ ቱዩብ

Friday, January 16, 2015

አንድ…ሶስት




አራት በአራት በሆነች ክፍል ውስጥ ረሃ እየሆኑ ነው፡፡ አንዱን ሲጥሉ አንዱን ሲያነሱ ታላቅ የአሳብ ባህር ውስጥ ገብተው ስለሕይወት ይፈላሰፉ ጀምረዋል፡፡ የፊት ገፅታቸው ተቀያይሯል….አይኖቻቸው ልውጣ ልውጣ የሚሉ ይመስላሉ፡፡ ፈጠዋል፡፡ የቤቱ ሙቀት የሲጋራው ጢስ ታክሎበት ፊትን ይጋራፋል፡፡ ሶስት ብቻ በመሆናቸው ተጠባብቆ ለማውራት አመችቷቸዋል፡፡የማህበረሰቡን ወግ መኮነን ተያይዘውታል፤ከግለሰብ ማንነታቸው ጋር ሊሄድ ባልቻለው ማህበረሰብ ውስጥ ተፈጥረው ማድረግ የፈለጉትን የሞራል ሕግ በሚል ጠፍሮ የያዛቸውን የቡድን ሕግ በማውገዝ ላይ ናቸው፡፡ ሞራል ደካሞችና ፈሪዎች ጠንካሮችን የሚያስሩበት ሰንሰለት መሆኑን መተማመን ችለዋል፡፡ The only good man is the man who succeeds የምትለዋ የኒቼ አሳብ አጥንታቸው ድረስ ዘልቆ ተሰምቷቸዋል፡፡ አሸናፊዎች ሁሌም ጉዞ ላይ ናቸው፤በጉዞው የደከሙትና መረሳት ያልፈለጉት የሞራልን ጉዳይ በማንሳት በጉዞዋቸው ርቀው እንዳይሔዱ ያደርጋሉ በዚህም በማህበረሰብ ውስጥ የሚበቅሉ አሸናፊዎች ነገራቸው ሁሉ ከማህበረሰቡ አመለካከት አንጻር እየተለካ ለውግዘትና ለመገለል ያበቃቸዋል፡፡
      ትምህርቷን ከአስራ ሁለተኛ ክፍል አቋርጣ ቤት ብትውልም መፅሐፍትን የማንበብ ክፉኛ መንፈስ ተጠናውቷታል፡፡ ማንንም ተናግሮ ማሳመን የተካነችው ለግላጋዋ ወጣት በሁለት ወንዶች መሃል ወሲብን ማውራት የቀለለ ተራ ነገር አድርጋዋለች፡፡ የሁለቱን ወጣቶች ጆሮ ለጉድ ተቆጣጥራዋለች፡፡ ታወራለች፤ይሰሟታል፡፡

Friday, January 9, 2015

ባህረ ሃሳብ

                   
አየሩ ለዐይን ይይዛል….በብርሃን ነፀብራቅ ውበታቸው የሚገዛን የቀኑ ሙሽሮች ጠቆርቆር ብለዋል፡፡ ለወትሮው በሚያማምር የብረት ዘንግ ተከበው በንፋሱ ግፊት ጣፋጭ በሆነው ለስላሳ ሙዚቃ የሚወዛወዙ አዲስ ሙሽሮች የሚመስሉት ዛፎች ውበታቸው ደብዝዞ ፀጥታ ውጧቸዋል፡፡በአርምሞ ላይ ይመስላሉ፡፡ በዚህ የፀጥታ ወጀብ በፀጥታ መንጎዱ አስፈራኝ፡፡ ይልቅ ከእጅ ስልኬ ላይ ዘፈን ከፍቼ መመሰጡን ምርጫዬ አደረኩት፡፡
     የኔ ፍቅር….ለካ እንዲህ እወድሻለው
     አብረን ሆነን መች አስቤው አውቃለው…….
ሙዚቃው ነው፡፡ እንደወትሮው የሙዚቃው መሳሪያ ቀድሞ ዘፋኙ ይከተላል ስል ዘፋኙ ቀድሞ መሪ ሆኖ አረፈው፡፡ የልጅ የመሰለ ቀጭን ድምፅ ሞቅ ብሎ ጆሮ ላይ ሲስረቀረቅ እንደ ጅብ ጥላ ከብዶ ሰብሰብ ብሎ የነበረው ደመና በሞቅታው ሲበታተን…የሞቀው አየር በአፍንጫዬ ቁልቁል ይተም ጀመር፡፡ ሞቅ አለኝ፡፡ ዙሪያዬን ከበው የሚያዜሙልኝ መላህክትን ያየው ያህል ደስ አለኝ፡፡
     ዳገቱን ጨርሼ አውራ ጎዳናውን ተቀላቀልኩት፡፡ ዘፋኙ መዝፈኑን ቀጥሏል፡፡
          እንዲህ ይጨንቃል ሆይ አንቺን መሸኘቴ
          ባዶ አረግሽኝ የእኔ አመቤቴ
          ሳይታሰብ በድንገት
ልክ ልኬን እየነገረኝ መሰለኝ….ደነገጥኩኝ…ከሳምንት በፊት ዘግቼው የነበረው አጀንዳ በእሊና የፍትህ ጓዳ ተቀሰቀሰ፡፡ ማን ይግባኝ ጠየቀ? ታሳሳኝ የነበረችው የጠዋቷ ፀሐይ የልቤን ንግስት ላላስጨንቃት ለራሴ ቃል ገብቼ ነበር፡፡

በልደቴ ቀን….


ዛሬ ኢየሱስ ተወልዷል፡፡ ልደቱን በሚገባ ላከብርለት እንደሚገባ እያንሰላሰልኩ ነው፡፡ ዛሬ ልዩ መሆን እንደሚገባኝም ይሰማኛል፡፡ የናርዶሱ ሽታ የናዝሪቱ ኢየሱስ…..የፍቅር አባት…..ዛሬ ምድርን እረገጣት፡፡ የምድር ላይ የመጀመሪያውን ሰከንዶች በለቅሶ ጀመረው፡፡ የሠላሙ አለቃ ሠላማችንን ሊሰጥ ለጥያቄያችን መልስ ይዞ በእናቱ እቅፍ ሆኖ እያለቀሰ ይህችን መራራ አለም ተቀላቀላት፡፡
     ጨቋኟ፣ቅብዝብዟ አለም አደቧን ልትገዛ ሰላሟን በበረት ተቀበለችው፡፡ ለሰላሟ ማረሻ የሚሆን ቦታ ጠፍቷት ስትባዝን ግርግም የነበረው ሠላሟ የከብቶችን ትንፋሽ ይሞቅ እንደነበር እንኳን ሳታስተውል ቀረች፡፡ ፍቅራችን ኢየሱስን ልታሞቀው በጨርቅ ጠቀለለችው…..የሠላም እናት የፍቅር መገኛ ንፁኋ ማሪያም፡፡ ደጉ ኢየሱስ አውን ምድር ላይ ነው፡፡ እንደሰው እንኖር ዘንድ፤ሰውን መሆን ሊያስተምረን ህፃኑ ግርግም ውስጥ ከከብቶች መሃል በጨርቅ ተጠቅልሎ ቅርጫት ውስጥ ተኝቷል፡፡ የአባቶች ምኞት፣የነቢያት ትንቢት፣የዳዊት የመዝሙሩ ቃና፣የስምኦን ናፍቆት መድሃኒት ዛሬ መጣልን፡፡
     ይህን በማውጠንጠን ላይ ሳለው የጓደኛዬ የእጅ ስልክ ያቃጭል ጀመር፡፡ አሳቤን ለሰከንዶች ገትቼ ዙሪያዬን እቃኝ ገባው፡፡ ሁሉም ውብ ነው፡፡ የሠላም ነፋስ፣የፍቅር ሙቀት፣የጠራ አየር….የአህዋፋት በረራ በራሱ ፍፁም ውበትን አይበት ጀመር፡፡ ከሩቅ የምሰማው የጉጉት ድምፅ ከዛፎቹ የአርምሞ እንቅስቃሴ ጋር ተደምሮ የማላውቀውን ዜማ ፈጥሮ ጭንቅላቴ ላይ ይጫወታል፡፡ ሙሉዋ ጨረቃ የዛሬውን ያህል አልደመቀችብኝም፡፡ ፀሐይዋን ለማሸነፍ ትግል ገጥማ የነበረችው ጨረቃ በሞት ሽረት ትግሉ የተሰነዘረባት የፀሐይ ጨረር ውበቷን ይበልጥ አፍክቷታል፡፡ እይታዬን የገታኝ ከፊት ለፊቴ የሚመጣው ሞርሳሳው ውሻ ነበር፡፡ ሞሪስ…የውሻው ስም ነው…አመጣጡ ለልፊያ እንደሆነ ያስታውቃል፡፡ ልብሴን እንዳያበላሽብኝ ፈንጠር ብዬ አስቀድሜ ተነሳው፡፡ እንደወትሮው ጭራውን ወደላይ አኮፍሶ ያርገበግበዋል…ደስ ብሎታል፡፡ የሞሪስን የደስታውን ምንጭ ባላውቅም ቅብጥብጡን ውሻ አይቼ ቀኑን አሰብኩት፡፡ ሃስብ ወደነበረው ወደቀደመ ሃሳቤ ተመለስኩ፡፡

Sunday, December 22, 2013

የሮበርት አንቶኔ ሕይወትን የመቀየሪያ ምስጢሮች

የአንድ ሺህ ማይል ጉዞ መጀመሪያው አንድ እርምጃ ነው የሚለውን አባባል ሰምተው ሊሆን ይችላል፡፡ እርሶም ይህን አንድ እርምጃ በመጀመርሆ እንኳን ደስ አልዎ!
እንደብዞዎች አኗኗር ስልት ከሆነ ሕይወትዎ በጣም የተጨናነቀና ውጥረት የበዛበት ነው፡፡ ቢሆንም እባክሆ ለሚቀጥሉት ስድስት ቀናት ጊዜዎት ሰተውኝ ይህን ፅሁፍ ያንብቡልኝ፡፡
ምን አልባት ነገሬን ሳልጀምር ስለምን ላወራ እንደሆነ ገምተው አሊያም ሙሉ በሙሉ አውቀውት ሊሆን ይችላል፡፡ እባክሆ ሙሉ ፅሁፉን አንብበው ሳይጨርሱ ምንም አይነት ፍርድ ለመስጠት አይቸኩሉ፡፡
እንጀምር…..
ነገሬን በጥያቄ ልጀምር " ይህን ፅሁፍ ለምን እንደሚያነቡት ያውቃሉ?"
ምንአልባት መልስዎ ሊሆን የሚችለው "ባጋጣሚ ብሎግህን ሰርች ሳደርግ አግኝቸው ነው" አሊያም "ጓደኛዬ ስለዚህ ፅሁፍ መረጃ ሰቶኝ ነው" ወይም የተለያዩ አመክኖአዊ መልሶችን ሊሰጡኝ ይችላሉ፡፡
ዋናው ነገር መልስዎ አመክኖአዊ ይሁንም አይሁንም ይህን ፅሁፍ የሚያነቡበት መሰረታዊ ነገር እንዳለ እሙን ነው፡፡ አንድ ነገር እየፈለጉ ነው! ነገር ግን እስከ አሁን ድረስ በእይወትዎ ላይ ሊያመጣ ያለውን ነገር አላስተዋሉትም፡፡
ይህ ፅሁፍ ለእርስዎ የሚሰጠው አንድ ነገር አለ ምናልባት በንግድ፤በጤናዎ፤በፍቅር እይወትዎ አሊያም ሊታይ የማይችል የአይምሮ ደስታ፡፡
አዕምርዎ በሕይወትዎ  ውስጥ የፈለጉትን ሊያገኙበት የሚችሉበት ዋንኛውና ትልቁ ጉልበትዎ እንደሆነ እስከ አሁን አልነገርኮትም፡፡ ሁሉም ሰው ጭንቅላት አለው ነገር ግን ስለምን አዕምሯቸውን ተጠቅመው የሚያልሙትን ሕይወት መኖር ተሳናቸው?
ለምን ብዙ ሰዎች የአዕምሯቸውን ጉልበት ለራሳቸው ከመጠቀም ይልቅ እራሳቸውን ለማጥፊያነት ይጠቀሙበታል? መልሱን ከጥቂት ደቂቃ በኋላ ያገኙታል፡፡ ትግስትዎ አይለየኝ፡፡

Wednesday, November 13, 2013

ዳግማዊ ሠለሞን!

መቼም ስለ መርካቶ ያልተወራ ነገር ያለ አይመስለኝም….መርካቶን የማያውቃት ይኖራል ለማለትም አልደፍርም፡፡ ከአፍሪካ በስፋቱ ተወዳዳሪ ያልተገኘለት ትልቁ የገበያ ማህከል፡፡መርካቶ!
ስለ መርካቶ ሎሬት ፀጋዬ ገ/መድህን በግጥም ‹‹አይ መርካቶ›› ተወዳጁ አብዱ ኪያር በዜማ ‹‹መርካቶ ሰፈሬ›› ና ወዘተ የብዙ የጥበብ ሰዎች እጅ ዳሷታል፡፡
እኔ የምለው መርካቶ ውስጥ ካሉ ቦታዎች አውቶብስ ተራ አካባቢ የሚገኘውን አዲስ ከተማ ት/ቤትን አስተውለውት ያውቃሉ?
የቀድሞ ልዑል መኮንን የአሁኑ አዲስ ከተማ መሠናዶ ት/ቤት የሠፈረበት አካካባቢ አስገራሚ ገፅታ ያለው ቦታ ነው፡፡ ት/ቤቱን ለተመለከተው እንዴት ሰው ሊማርበት ይችላል ብሎ ሊገረም እንደሚችል ጥርጥር የለኝም፡፡ እመኑኝ በድፍን ኢትዮጵያ እንደ አዲስ ከተማ አስገራሚ ት/ቤት አይኖርም፡፡
ቀን በእውቀት የታነፁ የአገር ተረካቢዎችን ለማፍራት የሚታትረው ት/ቤት ማታ ማታ በብዙ እንስቶች ተከቦ ይታያል፡፡
አንዳንዴ ዝም ብዬ ስመለከተው ጠቢቡ ሰለሞንን የሆነ ይመስለኛል፡፡ ምክንያቱም ሁለቱም በሴት የመታጀባቸው ጉዳይ ነው፡፡
የዘመኑ ሰለሞን አዲስ ከተማ አመሻሽ ላይ ልጅነታቸውን ባልጨረሱ ወጣት ሴቶች ተከቦ ማየቱ የተለመደ ነው፡፡

Saturday, May 25, 2013

የቡርቃ ዝምታ የተሰኘውን መፅሐፍ በነፃ ያነቡት

ጋዜጠኛና ደራሲ ተስፋዬ ገብረአብ 
ከታዋቂውና ዝነኛው ጋዜጠኛና ደራሲ ተስፋዬ ገብረአብ መፅሐፎች ውስጥ የቡርቃ ዝምታ የተሰኘውን መፅሐፍ በነፃ ያነቡት ዘንድ ተጋብዘዋል፡፡

Friday, May 24, 2013

A Little Joke


The pope dies and goes to heaven. At the pearly gates, St. Peter welcomes him and asks if he's ready to enter heaven for all eternity. The pope replies, "Yes, but before I go in, I would really like to see what hell is like."
St. Peter thinks a moment and then responds, "I suppose it would be okay if you went down there for a half hour or so."
With that, the pope finds himself in hell, where, to his amazement, the inhabitants are having a huge party. They have the best of the best spread out: French champagne, Italian food, and music of all sorts, from Lawrence Welk to Jimi Hendrix. As the pope watches everyone eating, drinking and being merry, he starts to become very hungry and cannot wait to go back to heaven.
When the pope returns, St. Peter asks him, "How was hell?"
The pope replies, "Well, they were having such a big feast, I became famished watching them."

Friday, May 3, 2013

ፋሲካና ዶሮ


የፋሲካ በአል የአበሻ ምድር ላይ በተለየ መልኩ ከሚከበሩ በአላት ግንባር ቀደሙ ነው፡፡ ይህን በአል ለየት የሚያደርገው ለአርባ ቀናት ከስጋና መሰል ምግቦች ተከልክሎ የከረመው የምህበኑ ሰውነት በአንድ ቀን ለሊት ውስጥ ያለ የሌለ አቅሙን አፈርጥሞ ለበቀል ሆዱን የሚያሰፋበት፤የእጆቹን መዳፍ  በቅባት የሚያረሰርስበት በአጠቃላይ ዶሮ በተባለች አዕዋፍ (እንስሳት) ላይ አብዮት የሚፈነዳበት የአብዮት በአል ነው፡፡ ወዳጄ የተሰመረባትን ሐረግ ሌላ ፍቺ እንዳይሰጧት እማጸኖታለው፡፡ ምናልባት በአሉ የድህነት እንጂ የአብዮት አይደለም ብሎ ሊሞግት የሚነሳ ካለ ባይደክም ጥሩ ነው፡፡ ምክንያቱም ሙሉ በሙሉ የደህንነት በአል ለመሆኑ በሙሉ ልቤ አማኝ ስለሆንኩ….
ፋሲካችን ክርስቶስ በእለተ አሙስ ተይዞ ለፍርድ ወደ ጲላጦስ አደባባይ በሚወሰድበት ወቅት ለሚወደው ደቀ መዝሙሩ ዶሮ ሳይጮህ ሶስት ጊዜ ትክደኛለህ ብሌ ቀድሞ ተናግሮት እንደነበር ቅዱስ መፅሐፍ ይነግረናል፡፡ ቅዱሱ ሰው፤የቤተ ክርስቲያን የአለት መሰረት ታላቁ አዋርያ ጌታውን አላውቀውም ብሎ ሲክደው የክርስቶስን ቅድሚያ ትንቢት የቅዱስ ጴጥሮስን ክህደት ቆጥራ የመሰከረች ይህች ዶሮ ዛሬ ላይ ክፉኛ ተጨቁና ለፆም መፈሰኪያ መዋሏን ስናይ (በተለይ ለአቢሲኒያውያን) ነገሩ ምን ያህል ትስስር እንዳለው እንረዳለን፡፡ በቅዱስ ጴጥሮስ ፊት አውራሪነት የተመሰረተችው ቤተ ክርስቲያን ምዕመኖቿ ፋሲካቸውን በዶሮ መፈሰካቸው ምናልባትም ለምን አሽቃበትሽ በሚል የበቀል እርምጃ እየተወሰደባት ለመሆኖም ግምት ሰቶ ማለፍ ይቻላል፡፡

Wednesday, April 24, 2013

የኢሰፓ ሊቀመንበር የነበሩት ኮሎኔል መንግስቱ በልብ በሽታ .መሞት.....



menegestu
Mengestu h/mariam with Fidel kastero
የዛሬ የማህበራዊ ድህረ ገፅ ወሬዎች በቀድሞ የኢሰፓ ሊቀመንበር በነበሩት ኮሎኔል መንግስቱ ሃ/ማርያም ሆኗል፡፡ ኮሎኔሉ በልብ በሽታ እነደሞቱ ጥቂት የማይባሉ የማህበራዊ ድህረ ገፅ ታዳሚዎች መርዶውን እየነገሩን ነው፡፡ የኮሎኔሉን መሞት መንግስት ከዘረጋው መልካም አስተዳደር የመነጨ ስለመሆኖም አንዳንዶች እየደሰኮሩ ስንሰማ ባላንጣችንን ሞት ክብር ላንተ እንድል አስገድዶናል፡፡ መንግስቱ ደግም ሰሩ ክፉ የዚህች ድሃ አገር ገዥ ሆነው ለ 17 አመታት ኖረዋል፡፡ በመሞታቸው መደሰት ሳይሆን እንሲቪላይዝድ ሰው ቤተሰባቸውን ባናፅናናም ክፉ መናገሩን በበኩሌ የማልደግፈው ነው፡፡ አትዮጵያ ባትቀድምም አትዮጵያ ትቅደምን እንድናዜም ያረጉ ሶሻሊስት ኢትዮጵያን ለመገንባት ግንባር ድረስ የሄዱ ትጉህ ወታደር ኋላም ጥሩ ፈርጣጭ ነበሩና የእውነት ሞተው እንኳን ቢሆን ነብሳቸውን ይማርልን ብለን ኢትዮጵያዊ ጨዋነታችንን እናሳይ እላለው፡፡

Sunday, April 14, 2013

አበሻ ኩሩ ነው!?

የትኛው አበሻ? የድሮው ወይስ የአሁኑ? እውን በምናችን ይሆን እንዲ አበሻ ኩሩ ነው በሚል ብሂል ውጥርጥር ያልነው፡፡ ቲሸርቶቻችን የሚናገሩት ስለኩሩነታችን፤ስለጀግንነታችንና ስለብዝሃነታችን ከሆነ ሰንበትበት ብሏል፡፡ኩሩ ማህበረሰብ ለራሱ የተለየ ቦታ ያለውና ሌሎች ላይ የማይደርስ በሎሎች የተከበረ ለመሆኑም የማህበረሰብ ሳይንስ ሊቃውንት የሚስማሙበት አቅ ነው፡፡
የአበሻ ኩሩነት እንደቻይናውያን እንቁራሪት አለመብላቱና ምግብ መምረጡ ከሆነ ኩሩነት ትርጉሙ መቀየር አለበት ባይ ነኝ፡፡ ኩሩነታችን አለመንበርከካችንና በነጭ አለመገዛታችን  ነው የምንል ከሆነ ደግሞ ለዚህ ዘመን አበሾች የማይመጥን ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ ነጮች እንደዋዛ ክብራችንን ከነጠቁን ዘመናት አለፉ....በቱሪስት መዳረሻ በሆኑ ከተሞቻችን  ኩሩው አበሻ ለፈረንጆች የሚያሳየውን ፍቅር ስንመለከት ሰውኛ የሆነ የጨዋ ሕዝብ ልዩ ምልክት መሆኑን እንታዘብና ወደራሳችን ተመልሰን ጓዳችንን ስናይ የሰውኛ ባህሪ መሆኑ ይጠፋብንና አድር ባይነታችን ይጎላብናል፡፡ ሴቶቻችን የአበሻ ወንድ በአፍንጫዬ ካሉም ሰንበትበት ብለዋል...ቄሶቻችን በቤተ እምነት መዘክር ውስጥ ‹‹ፈረንጅ መቷል ውጡ›› ማለት ከጀመሩም አመታት አለፉ፡፡ ማለፍ ክልክል ነው፤መንገዱ ዝግ ነው በሚባሉ ቦታዎች ላይ አበሾች ተኮልኩለው ነጭ እንደዋዛ ሲያልፍና ፍቃድ ሲሰጠው ስናይ ልማታዊነታችን ታውሶን በቸልታ የምናልፈው የእለት ተእለት ተራ ጉዳይ ከሆነም ሰንብቷል፡፡ ኩሩነት በአባቶች ታሪክ መታበይ ከሆነ እውነት ኩሩ አለመሆናችንን ላስረግጥ እወዳለው፡፡
የአበሻ ኩሩነት በጎዳና የወደቀውን ወንድሙን የሚያንቋሽሽና አለውልህ ከማለት የኘጮችን በጎነት የሚናፍቅ እከሌ እኮ እስፖንሰር አግኝቶ....የምንል የጉድ ልጆች ከንቱ ኩራት... ሲረግጡን የምንረገጥ የራሳችን ማንነት የጠፋብን ተአምር ጠባቂዎች፤የምላስ ቁማርተኞች፤ሆዳችን ክብራችን የሆነ ዘመነኛ ኩሩዎች!
ወዳጄ ኩሩ ነኝ ብለህ ታስባለህ? እንግዲያውስ ለራስህ ቦታ ይኑርህ፤እራስህን አክብር፤ በቆዳ ልዩነት የማታምን ቅድሚያ ለኢትዮጵያዊው ወንድሜ የሚል አትዮጵያዊ ብሔርተኛ ሁን!!
በዚህ ርዕሰ ጉዳይ ላይ ወደፊት በሰፊው እናወጋለን፡፡

Tuesday, April 9, 2013

የሕዝብ ልጅ ምንግዜም የሕዝብ ነው!

Temesgen desalghe
የሕዝብ ልጅ ምንግዜም የሕዝብ ነው!
ግዛው ስለሺ ጃኖ መፅሔት ቅፅ 1 ቁጥር 2 ላይ የሰማኒያ አመቱ አዛውንትና የአምስት አመቱ ፈረሳቸው ብሎ የፃፈውን ፅሁፍ ላነበበ ሰው በእርግጠኝነት ስለፀሐፊው የሚኖረው አመለካከት የተዛባ ነው የሚሆነው፡፡አቶ ግዛው ማመዛን የከበደው ሰው ለመመሆኑም መስካሪ አያሻም፡፡ በግል ፕሬስ ማሊያ የሕዝብ ልጆችን ላማጥላላት ታጥቆ የተነሳ ባንዳ መሆኑን ከፅሁፉ ጭብጥ መረዳት አያዳግትም፡፡
የሰማኒያ አመት አዛውንት የተባሉት ፕሮፌሰር መስፍን በአምስት አመት በተመሰላው ተመስገን ደሳለኝ መፅሔትና ጋዜጣ ላይ የሚያወጡት መጣጥፎች የአንባቢን ቀልብ የሚስቡና ጠማማውን ለማቅናት የሚታትር፤ ገዥውን የሚያስተምር መሆናቸውን የዚህ ፅሁፍ አዘጋጅ በፅኑ ያምናል፡፡ እኚህ ምሁር በስተርጅና ፈርሆንን የሚቃወሙበት ምክንያት የስልጣን ጥማት ስላላቸው ነው ተብሎ የሚታመን እንኳን ቢሆን በፍትህ፤በአዲስ ታይምስ እንዲሁም የእሳት እራት በሆነችው ልህልና መፅሔት ላይ ቋሚ አምደኛ በመሆን የሚያወጧቸው ፅሁፎች የበሰሉ ትችቶችና ፍትህና ዲሞክራሲን ናፋቂዎች ለመሆናቸው ማንም ሊመሰክረው የሚችለው አቅ ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ አቶ ግዛው ስለሺ ምንም እንኳን ስለፕሮፌሰሩ የኋላ ታሪክ ቢነግረንም ምሁሩ ላይ ያለውን የመረረ ጥላቻ ያሳብቁበታል፡፡ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲና በመላው አገሪቱ በሚገኙ የትምህርት ተቋማት ውስጥ ያሉ ምሁራን ሊነግሩን ያልደፈሩትንና ከመሞት መሰንበት በሚል አገርኛ ብሂል አድር ባይነትን መርጠው አፋቸውን ለጉመው በተቀመጡበት ወቅታዊ የአገራችን ችግሮች ላይ እንዲሁም የታሪክ አመክንዮ ላይ እኚህ ምሁር የሠላ አስተያየቶችንና የተጣመመ የታሪክ አተያዮችን(ኢትዮጵያ የመቶ አመት ታሪክ ያላት አገር ነች እና የመሳሰሉትን) በማቅናትና እውነትን በመመስከር ለሚያበረክቱት አስተዋፅሆ ምስጋና መቸር ሲገባን የስልጣን ጥማተኛ አስመስሎ ማብጠልጠሉ ነገ ከአድር ባይነት ተላቀው በቀናነት ለመስራት ለሚነሱ ምሁራን ታላቅ እንቅፋት መሆኑ እሙን ነው፡፡

Thursday, March 7, 2013

Where did the Universe Come From? (prove to you that God exists" ) part 4




Where did the Universe Come From? 
Part 4: "If you can read this sentence, I can prove to you that God exists"




  Yeah, I know, that sounds crazy.  But I'm not asking you to believe anything just yet, until you see the evidence for yourself.  All I ask is that you refrain from disbelieving while I show you my proof.  It only takes a minute to convey, but it speaks to one of the most important questions of all time.

  So how is this article proof of the existence of God?:

  This article you're reading contains letters, words and sentences.  It contains a message that means something. As long as you can read English, you can understand what I'm saying.

Where did the Universe come from? part 3


Where did the Universe come from?
Part 3: Why the Big Bang was the most precisely planned event in all of history



  In your kitchen cabinet, you've probably got a spray bottle with an adjustable nozzle.  If you twist the nozzle one way, it sprays a fine mist into the air.  You twist the nozzle the other way, it squirts a jet of water
in a straight line.  You turn that nozzle to the exact position you want so you can wash a mirror, clean up
a spill, or whatever.

  If the universe had expanded a little faster, the matter would have sprayed out into space like fine mist from a water bottle - so fast that a gazillion particles of dust would speed into infinity and never even
form a single star.
   If the universe had expanded just a little slower, the material would have dribbled out like big drops of water, then collapsed back where it came from by the force of gravity.

  A little too fast, and you get a meaningless spray of fine dust.  A little too slow, and the whole universe collapses back into one big black hole.

  The surprising thing is just how narrow the difference is.  To strike the perfect balance between too fast and
too slow, the force, something that physicists call "the Dark Energy Term" had to be accurate to one part in
ten with 120 zeros. 
    If you wrote this as a decimal, the number would look like this:
0.00000000000000000000000000000000000000000000000000000000000000000000000000 000000000000000000000000000000000000000000000000001

  In their paper "Disturbing Implications of a Cosmological Constant" two atheist scientists from Stanford University stated that the existence of this dark energy term would have required a miracle..."An unknown agent" intervened in cosmic history "for reasons of its own."

Where did the Universe come from? part 2


Where did the Universe come from?
Part 2: "Bird Droppings on my Telescope"

  The Big Bang theory was totally rejected at first. But those who supported it had predicted that the ignition
of the Big Bang would have left behind a sort of 'hot flash' of radiation.

  If a big black wood stove produces heat that you can feel, then in a similar manner, the Big Bang should
produce its own kind of heat that would echo throughout the universe.

  In 1965, without looking for it, two physicists at Bell Labs in New Jersey found it.  At first, Arno Penzias
and Robert Wilson were bothered because, while trying to refine the world's most sensitive radio antenna,
they couldn't eliminate a bothersome source of noise. They picked up this noise everywhere they pointed the
antenna.
At first they thought it was bird droppings.  The antenna was so sensitive it could pick up the heat of bird droppings (which certainly are warm when they're brand new) but even after cleaning it off, they still picked up this noise.

Where did the Universe come from? part 1


this article wrote  by Perry Marshall <perry@cosmicfingerprints.com>
Part 1: Einstein's Big Blunder

  100 years ago, Albert Einstein publishes three papers that rocked the world.  These papers
proved the existence of the atom, introduced the theory of relativity, and described quantum
mechanics.

  Pretty good debut for a 26 year old scientist, huh?

  His equations for relativity indicated that the universe was expanding.  This bothered him, because if it was expanding, it must have had a beginning and a beginner.
Since neither of these appealed to him, Einstein introduced a 'fudge factor' that ensured a 'steady state' universe, one that had no beginning or end.

  But in 1929, Edwin Hubble showed that the furthest galaxies were fleeing away from each other, just as the Big Bang model predicted.  So in 1931, Einstein embraced what would later be known as the Big Bang theory, saying,
"This is the most beautiful and satisfactory explanation of creation to which I have ever listened."  He referred to the 'fudge factor' to achieve a steady-state universe as the biggest blunder of his career.

Sunday, February 10, 2013

ሃ/ማርያም ሆይ ጫማው ሰፍቶዎታል!!!

ሃ/ማርያም ሆይ ጫማው ሰፍቶዎታል!!!

የሠዎች አስተሳሰብ በኖሩበት ማህበረሰብ እንዲሁም በግለሰባዊ ማንነት ላይ ተመርኩዞ የተለያየ እንደሚሆን እሙን
ነው፡፡ከአንድ ማህፀን በወጡ ሁለት መንትያ ልጆች መካከል እንኳን የሚኖረው የአስተሳሰብ ልዩነት ስንመለከት ሠዎች
በየትኛውም መለከኪያ ተመሳሳይ የሆነ የአስተሳሰብ ደረጃ ሊኖራቸው እንደማይችል እንረዳለን፡፡ በአንድ ነገር ላይ
ተመሳሳይ አቋም ቢኖረንም ነገሩን የምንረዳበት መንገድና የአፈፃፀሙ ሁኔታ ከሰው ሰው ተለያይቶም እንመለከታለን፡፡
የአብዮታዊ ዲሞክራሲ ልሂቃን የሆኑት መሪዎቻችን በአንድ ልብ እናስብ በአንድ ቃል እናውራ ብለው መነሳታቸው
ምናልባትም በመንፈሳዊ ሕይወታችን የምናውቃቸው የቤተክርስቲያን ሊቃውንት ሰልስቱ ምዕት እንደ አንድ ልብ አሳቢ
እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ በመሆን በቤተክርስቲያን ላይ ክህደት የፈፀሙትን ሰዎች አውግዘው እንደነበር ድርሳናት
ያወሱትን እንድናስታውስ ይጋብዘናል፡፡ መቼም መለኮታዊ ሃይል ካልዳሰሰን በቀር ሠዎች በአመለካከትና በአነጋገር
ፍፁም አንድ ሆነው ያለአሳብ ልዩነት ነገሮችን ሊወስኑ እንደማይችሉ በቤተሰብ ውስጥ በሚወሰኑ ውሳኔዎች እንኳን
መታዘብ እንችላለን፡፡(ፈላጭ ቆራጭ አባወራ ካልሆነ፡፡)
ላለፉት 20 እና 21 አመታት ውስጥ በኢትዮጵያ ፓርላማ ውስጥ ነገሮች ሲወሰኑ መለኮታዊ ሃይል የዳሰሳቸው ይመስል
ያለ አንዳች ክርክርና ተቃውሞ ውሳኔዎች ሲወሰኑ አይተናል፡፡መቼም ያለአሳብ ልዩነት ጥሩ ነገር ማግኘት አይቻልም
እንዲሁም የተሻለውን መወሰን ፍፁም ከባድ መሆኑንና ተከትሎት የሚመጣውም ውጤት አስደሳች እንደማይሆን መረዳቱ
አስቸጋሪ አይሆንም፡፡ አምባ ገነኖች ለሚያነሱት አሳብ ተቃውሞን እንደማይሹ የፓርላማ ውስጥ ሽሙጥና ዘለፋ ምስክር
ነው፡፡በአለም ላይ ስልጣን የያዙ አምባገነን መሪዎች ሁሉ ተመሳሳይ የሚያደርጋቸው ባህሪ ቢኖር ለሕብረተሰቡ
እናውቅልሃለን፤እኛ ከሌለን…የሚሉ ፈሊጦችን በአደባባይ መፎከር ነው፡፡አብዮታዊ መሪዎቻችን ቢሆኑም ለኢትዮጵያውያን
እናውቅልሃለን ከማለት ውጭ ፍላጎታችንን ጠይቀውን አያውቁም፡፡በየቀበሌው የሚደረገው ሕብረተሰባዊ ተሳትፎ
የሚያሰፈልገው ስብሰባም ቢሆን ፖለቲካዊ ፋይዳው እንጂ ለህብረተሰቡ የሚያስገኘው አንዳችም ኢኮኖሚያዊም ይሁን
ማህበራዊ ጥቅም እንደሌለ ኑሮዋችን በቂ ምስክር ነው፡፡
የሆነው ሆኖ መጤው ጠ/ሚንስትር የቀድሞውን ጠ/ሚንስትር ጫማ በማጥለቅ የግል ባህሪያቸውንና ውስጣቸው የተደበቀውን
ሃይል እያጠፉ ያለ ይመስለኛል፡፡ ሠው እንደራሱ እንጂ እንደጎረቤቱ አይኖርም የሚለው ኢትዮጵያዊው ብሂል እዚህ
ጋር ወሃ ቋጥሮ እናገኘዋለን፡፡አቶ ሃ/ማሪያም እንደራሳቸው እንጂ እንደ አቶ መለስ ሊመሩን ከቶውንም አይገባም፡፡
እንደሚታወቀው የአቶ መለስ ጥንካሬ ፓርቲያቸውን ጠንካራ ከማድረግ አልፎ የሚኒሊክን ቤተ መንግስት የግላቸው
እስከማድረግ አድርሷቸዋል፡፡ ደግም ይሁን ክፉ በታጋዩ ፈርሆን የግል አመለካከትና ጥንካሬ አገሪቷ ላይ ለ21
አመት  ያሻቸውን ሲፈፅሙ እንደነበር የወራት ትዝታችን መሆኑን ከሞቱ በኋላ በትግል ጓዶቻቸው
ተመስክሮላቸዋል፡፡አቶ መለስ ከአልባኒያን ስርዓት እስከ ልማታዊ መንግስትነት ያደረሳቸው የራሳቸው የግል
አመለካከትን በለሌች ላይ በተለይ በትግል ጓዶቻቸው ላይ የማሳረፍ ታለቅ ተሰጥሆ ስለነበራቸው ነው፡፡(የአብዮታዊ
ዲሞክራሲ ልሂቃን ትግላቸው የአልባኒያ አይነት ስርዓት በኢትዮጵያ ለማምጣት እንደነበር የምንዘነጋው
አይደለም፡፡የሚገርመው ነገር መገንባት የሚፈልጉት ስርሃት ጨቋኝ በሚባለው መንግስቱ እንኳን የማይደገፍ መሆኑ
ነው፡፡በወቅቱ አልባኒያ በሆጃዎች ትመራ የነበር ፍፁም አምባ ገነንነት የሰፈነባት አገር ነበረች፡፡)