Wednesday, April 24, 2013

የኢሰፓ ሊቀመንበር የነበሩት ኮሎኔል መንግስቱ በልብ በሽታ .መሞት.....



menegestu
Mengestu h/mariam with Fidel kastero
የዛሬ የማህበራዊ ድህረ ገፅ ወሬዎች በቀድሞ የኢሰፓ ሊቀመንበር በነበሩት ኮሎኔል መንግስቱ ሃ/ማርያም ሆኗል፡፡ ኮሎኔሉ በልብ በሽታ እነደሞቱ ጥቂት የማይባሉ የማህበራዊ ድህረ ገፅ ታዳሚዎች መርዶውን እየነገሩን ነው፡፡ የኮሎኔሉን መሞት መንግስት ከዘረጋው መልካም አስተዳደር የመነጨ ስለመሆኖም አንዳንዶች እየደሰኮሩ ስንሰማ ባላንጣችንን ሞት ክብር ላንተ እንድል አስገድዶናል፡፡ መንግስቱ ደግም ሰሩ ክፉ የዚህች ድሃ አገር ገዥ ሆነው ለ 17 አመታት ኖረዋል፡፡ በመሞታቸው መደሰት ሳይሆን እንሲቪላይዝድ ሰው ቤተሰባቸውን ባናፅናናም ክፉ መናገሩን በበኩሌ የማልደግፈው ነው፡፡ አትዮጵያ ባትቀድምም አትዮጵያ ትቅደምን እንድናዜም ያረጉ ሶሻሊስት ኢትዮጵያን ለመገንባት ግንባር ድረስ የሄዱ ትጉህ ወታደር ኋላም ጥሩ ፈርጣጭ ነበሩና የእውነት ሞተው እንኳን ቢሆን ነብሳቸውን ይማርልን ብለን ኢትዮጵያዊ ጨዋነታችንን እናሳይ እላለው፡፡

1 comment: